አርሰናል በሜዳው አስቶንቪላን ገጥሞ አቻ ተለያይቷል። ጨዋታው ሁለት አቻ ተጠናቅቋል።
ቀደም ብሎ በተደረጉ ጨዋታዎች የሊጉ መሪ ሊቨርፑል ድል ቀንቶታል። ከሜዳው ውጭ ብሬንትፎርድን የገጠሙት ቀዮቹ 2ለዐ በማሸነፍ መሪነታቸውን አስፍተዋል።
ኒውካስትል በበርን ማውዝ፣ ዌስትሃም በፓላስ እንዲሁም ሌስተር በፉልሃም በሜዳቸው ተሸንፈዋል።
ሊጉን አንድ ተስተካካይ ጨዋታ የሚቀረው ሊቨርፑል በ50 ነጥብ ይመራዋል። አርሰናል በ44 ነጥብ ይከተላል።