ዋይኒ ሩኒ በውጤት ማጣት ከፕለይማውዝ እግር ኳስ ክለብ ጋር ተለያየ።

0
176

ባሕርዳር: ታኅሣሥ 22/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ዋይኒ ሩኒ ከፕለይማውንዝ ጋር ከሰባት ወራት በኋላ ተለያይተዋል። የ39 ዓመቱ የቀድሞ የእንግሊዝ አምበል ዋይኒ ሩኒ በክለቡ በነበረው ቆይታ 23 ጨዋታዎችን አድርጎ በአራቱ ብቻ ድል ሲቀናው በ13ቱ ደግሞ ተሸንፏል። በስድስት ጨዋታዎች ደግሞ አቻ ተለያይቷል።

ዋይኒ ሩኒ በነበረው ቆይታም ውጤታማ ጊዜን ባለማሳለፉ ነው ክለቡን ለመልቀቅ የተገደደው። ሩኒ እሑድ ዕለት በኦክስፎርድ ዩናይትድ 2-0 መሸነፉን ተከትሎ አሠልጣኙ በዘጠኝ ጨዋታ ያለ ምንም ድል ባደረገው ጉዞ ከደጋፊዎች ከፍተኛ ተቃውሞ ደርሶበታል።

ሩኒ ከሽንፈቱ በኋላ የተሰነዘረውን ትችት እንደማይቀበለው ተናግሯል። ይህን ተከትሎ ከክለቡ ጋር በስምምነት ተለያይቷል።

ዋይኒ ሩኒ ወደ አሠልጣኝነት ከመምጣቱ አስቀድሞ በተጫዋችነት ዘመኑ ለእንግሊዝ እና ለማንቸስተር ዩናይትድ በመጫዎት የጎል ሪከርዶች ባለቤት መኾን የቻለ ተጫዋችም ነበር።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here