የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዘጠነኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ።

0
244

ባሕር ዳር: ኅዳር 20/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በድሬዳዋ ስታድየም እየተካሄደ የሚገኘው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዘጠንኛ ሳምንት ላይ ደርሷል።

በቀን ሁለት ጨዋታዎችን እያካሄደ የሚገኘው ፕሪምየር ሊጉ ዛሬም ጨዋታዎችን ያካሂዳል። አዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር የሚያደርጉት ጨዋታ ደግሞ ቀዳሚው ጨዋታ ነው። ጨዋታው ቀን 10:00 ላይ ይካሂዳል።

የእለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ደግሞ አርባምንጭ ከተማን ከመቻል ያገናኛል። ከኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ሸር ካምፓኒ የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው ጨዋታው ምሽት 1:00 ላይ ይካሄዳል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here