ባሕር ዳር: ኅዳር 09/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የቶትንሃሙ ተጫዋች ቤንታኩር ቅጣት የተጣለበት የቡድን አጋሩ ሰን ሆንግ ሚን ላይ ዘር ላይ ያተኮረ ሃሳብ በመስጠቱ ነው።
ቤንታንኩር በቃለ መጠይቅ ወቅት ሰንን ጨምሮ የአጎት እና የአክስት ልጆቹ በመልክ አንድ አይነት ናቸው የሚል ሃሳብ ማንሳቱ ነው ለቅጣት ያበቃው።
የእንግሊዝ እግር ኳስ ማኅበር ተጫዋቹን ከሰባት ጨዋታ በተጨማሪ የ100ሺህ ዶላር ቅጣት ማስተላለፉን ቢቢሲ አስነብቧል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!