ባሕር ዳር: ጥቅምት 06/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ከሳውዝጌት በኋላ በጊዚያዊ አሠልጣኝ ሊ ካርስሊ እየተመራ ነው። ጎን ለጎን የሀገሪቱ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ቋሚ አሠልጣኝ ለመቅጠር አማራጮችን ሲያማትር ከቆየ በኋላ ቶማስ ቱሸልን ሾሟል። አንቶኒ ባሪ ደግሞ የቱሸል ምክትል አሠልጣኝ ኾነዋል።
ጊዚያዊ አሠልጣኙ ሊ ካርስሊ ቀጣዮቹን ሁለት የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታ እንደሚመሩም ታውቋል። ቱሸል ደግሞ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከጥር አንድ ጀምሮ ቡድኑን ይረከባሉ።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!