ወደ ብሔራዊ ቡድን የተመለሰው ሊዮኔል መሲ ምርጥ ብቃቱን አሳይቷል።

0
380

ባሕር ዳር: ጥቅምት 06/2017 ዓ.ም (አሚኮ)

አርጀንቲናዊ ኮከብ ሊዮኔል መሲ ከብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎች በጉዳት ርቆ ነበር። ነገር ግን በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ አርጀንቲና ከቦሊቪያ በነበረው ጨዋታ መሰለፍ ችሏል።

ሌሊት ከቦሊቪያ ጋር የነበረባትን ጨዋታ አርጀንቲና 6 ለ 0 አሸንፋለች። መሲ ሀትሪክ የሠራ ሲኾን ሁለት ግብ የኾኑ ኳሶችን ደግሞ አቀብሏል።

በተጨማሪም የጨዋታው ኮከብ ተብሎ የተመረጠው መሲ በህይወት ዘመኑ ያስቆጠራቸውን ግቦች ብዛትም 846 ደርሰዋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here