ባሕር ዳር: ሰኔ 13/2016 ዓ.ም (አሚኮ)
በኢንዞ ማርሴካ እየተመራ ወደ ፕሪምየር ሊጉ ያደገው ሌስተር ሲቲ አሠልጣኙ የቼልሲ አሠልጣኝ ኾነው መሾማቸው ይታወሳል።
ተተኪ አሠልጣኝ ፍለጋ ላይ የሰነበተው ሌስተር በመጨረሻ ስቲቭ ኩፐርን ሾሟል። ኩፐር ኖቲንግሀም ፎረስትን በማሠልጠን ከሁለት ዓመታት በፊት ወደ ፕሪምየር ሊጉ እንዲያደግ ባደረጉበት ሥራቸው ይታወቃሉ።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!