የጌዴኦ ባሕላዊ መልክዓ- ምድር በዩኔስኮ ተመዘገበ።

29

ባሕር ዳር: መስከረም 06/2016 ዓ.ም (አሚኮ) በሪያድ እየተካሄደ በሚገኘው 45ኛው የዓለም ቅርስ ኮሚቴ ጉባዔ ላይ በጌዴኦ ዞን የሚገኘው የጌዴኦ ባሕላዊ መልክዓ- ምድር በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሣይንስና የባሕል ድርጅት (ዩኔስኮ) ተመዘገበ፡፡

የቱሪዝም ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ለጉባኤው ዝርዝር ማብራሪያ አቅርበዋል። በጉባዔው ላይም ስለ ጌዴኦ ባሕላዊ መልክዓ-ምድር ዝርዝር ማብራሪያ ቀርቦ ውይይት ከተደረገበት እና አስተያየት ከተሰጠበት በኋላ ነው ምዝገባው የጸደቀው፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!